ሐምሌ 27/2018 ኢትዮጵያ 805 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል አዲስ የዓለም አቀፍ ሥነ ምህዳር ጥበቃ ታሪክ ባስመዘገበችበት ማግስት ባንካችን አቢሲንያ በእንጦጦ – አካባቢ ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለአደራ ተቋም ጋር በመቀናጀት የተለያዩ ሀገር በቀል ችግኞችን ተከላ መርሐ-ግብር አካሄደ::
የባንካችን ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና ሰራተኞች በዛሬው ዕለት ማለትም ሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ም እንጦጦ አካባቢ ልዩ ስሙ ፔንታጎን ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ላይ የተለያዩ ሃገር በቀል ችግኞችን ተከሉ፡፡ የባንካችን ዋና ፋይናንስ ኦፊሰር የሆኑት አቶ አብረሃም ገበየሁ እንደገለፁት ባንካችን ማኅበራዊ ...